በጉምሩክ ኮሚሽን የኮምቦልቻ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በተለያዩ ጊዜ ውርስ የተደረጉ ተሽከርካሪ ፣ የኮስሞቲክስ እቃዎች ፣ ከረሜላ ፣ SYTHETIC PIGMENT (አይረን ኦክሳይድ) ፣ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ፣ ልዩ ልዩ እቃዎች ፣ የቤት ቆርቆሮ ፣ ስታፋ ብረት አሮጌ ፕላስቲክና የፕላስቲክ ጫማ ፤ በግልፅ ጨረታ እንዲሁም መዳብ በሐራጅ ጨረታ ባሉበት ሁኔታ መሸጥ ይፈልጋል
Bid closing date
የጨረታው መዝጊያ ሰዓት በየሎቱ የተለያየ ነው
Bid opening date
የጨረታው መክፈቻ ሰዓት በየሎቱ የተለያየ ነው
Published on
አዲስ ዘመን
(Mar 28, 2024)
Posted
14 hours ago
Bid document price
100.00 ብር
Bid bond
በየሎቱ የተለያየ ነው
Region
በጉምሩክ ኮሚሽን የኮምቦልቻ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
የተጫራቾች ማስታወቂያ የጨረታ ቁጥር 20/2016 ዓ.ም
በጉምሩክ ኮሚሽን የኮምቦልቻ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በተለያዩ ጊዜ ውርስ የተደረጉ
- ተሽከርካሪ፣
- የኮስሞቲክስ እቃዎች፣
- ከረሜላ፣ SYTHETIC PIGMENT (አይረን ኦክሳይድ)፣
- የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች፣
- ልዩ ልዩ እቃዎች፣
- የቤት ቆርቆሮ፣
- ስታፋ ብረት አሮጌ ፕላስቲክና
- የፕላስቲክ ጫማ፤ በግልፅ ጨረታ እንዲሁም መዳብ በሐራጅ ጨረታ ባሉበት ሁኔታ መሸጥ ይፈልጋል።
በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የተጫራቾች መመሪያ የምታሟላ ተጫራቾች መወዳደር የምትችሉ ሲሆን ለተሽከርካሪው ማንኛውም እድሜው ከ8 ዓመት በላይ የሆነ መወዳደር ይችላል።
መስፈርቶቹ፡–
- በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች በጨረታ ከሚሸጠው ዕቃ ጋር ተዛማጅነት ያለው የፀና ንግድ ፈቃድ፣ የተጨማሪ ዕሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፍኬት እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማቅረብ የሚችል ግለሰብ መጫረት ይችላል።
- የዚህ አንቀፅ ተራ ቁጥር (1) ድንጋጌ ቢኖርም ግምታዊ ዋጋው ከብር 500 ሺህ በታች የሆነ ማንኛውንም እቃ ለመግዛት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስክር ወረቀት (ሰርተፍኬት) ማቅረብ አያስፈልገውም።
- በተጠቀሰው መስፈርት በጨረታ የሚሸጠው እቃ በኮሚሽኑ ቁጥጥር ስር ከመግባቱ በፊት ባለቤት የነበረ ወይም የባለቤቱ ወኪል ወይም ቤተሰብ የሆነ ሰው በማንኛውም መልኩ በጨረታው መሳተፍ አይችልም።
- ተጫራቾች የዕቃዎቹን ዝርዝር፤ ዓይነትና ብዛት የጨረታ ሰነድና መመሪያ እንዲሁም የጨረታ ዋጋ ማቅረቢያ ቅፅ የማይመለስ ብር 100 (አንድ መቶ) እየከፈሉ ኮምቦልቻ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የጉምሩክ ገቢ ሂሳብ ቡድን ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ስምንተኛው (8) ቀን 03፡00 ሰዓት ድረስ መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች ለጨረታው የዕቃዎችን ዝርዝር በያዘው ሰነድ ላይ ተጫራቹ የሰጠው ዋጋ በሚለው አምድ ሥር የሚገዙበትን ዋጋ በአሃዝና በፊደል ገልጸው በኤንቨሎፕ ወይም በፖስታ በማሸግ ጉምሩክ ኮሚሽን ኮምቦልቻ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በውርስ መጋዘን የሥራ ሂደት ቢሮ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ስምንተኛው ቀን 3፡50 ሰዓት ድረስ ማስገባት አለባቸው።
- የጨረታ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት በስምንተኛው ቀን በጉምሩክ ኮሚሽን ኮምቦልቻ ቅ/ፅ/ቤት በውርስ መጋዘን ቢሮ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚካሄድ ሲሆን ግልፅ ጨረታው 3፡50 ሰዓት ተዘግቶ 4፡00 ሰዓት የሚከፈት ሲሆን ሐራጅ ጨረታው 4፡45 ሰዓት የሚጀመር ይሆናል።
- ተጫራቾች በጨረታው አሸናፊ መሆናቸው ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ በ05 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ያሸነፉበት ዋጋ በመክፈል ንብረቶቹን ማንሳት ይኖርባቸዋል። በተሰጠው የጊዜ ገደብ ከፍለው የማይወስዱ ተጫራቾች ያስያዘ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (CPO) ለመ/ቤቱ ገቢ ተደርጎ እቃው እንደገና ለጨረታ ይቀርባል።
- ተጫራቾች ለእቃዎች በሚያቀርቡት የመጫረቻ ዋጋ አሸናፊ ከሆኑ ተጨማሪ ዕሴት ታክስ 15% (VAT) የሚጨመርበት ይሆናል።
- ተጫራቾች ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ሰባተኛው ቀን ድረስ ለሽያጭ የተዘጋጁ እቃዎችን በኮምቦልቻ ጉምሩክ ቅ/ፅ/ቤት በውርስ መጋዘን ቢሮ (አዲስ በሚሰራው– የጉምሩክ ህንፃ) በስራ ሰዓት ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት ከሰዓት በኋላ ከ8፡00 ሰዓት እስከ 10፡00 ሰዓት ድረስ እና በስምንተኛው ቀን ጠዋት 3፡00 ሰዓት ድረስ መመልከት ይችላሉ።
- ተጫራቾች ለግልፅ ጨረታ እቃዎች የሰጡትን የመግዣ ዋጋ አምስት በመቶ (5%) እና ለሐራጅ ጨረታ እቃዎች ሃያ አምስት ሺህ (25,000) ብር የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ከዋጋ ማቅረቢያ ቅፅ ጋር ማቅረብ አለባቸው።
- መሥሪያ ቤቱ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 033 551 06 93 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
በጉምሩክ ኮሚሽን ኮምቦልቻ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት